የሀዘን መግለጫ
በኢዜማ ፓርቲ አባል በአቶ ግርማ ሞገስ ለገሰ ላይ በቢሾፊቱ/ደብረ ዘይት ከተማ የተደረገውን የግድያ ወንጀል የባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ እጅጉን እንደሚያወግዘው እየገለፀ ለሟች ቤተሰብ እና ለባልደርቦቹ መፅናናትን ይመኛል፡፡
ብሄራዊ መግባባት ሽብር ባልፈጸመ ሰላማዊ ታጋይ ላይ የሽብር ክስ በመመስረት ህጉን የፖለቲካ ተገዥ በማድረግ አይገኝም!!!
“እውነት ከአንባገነኖች ክንድ ትበረታለች”! እናት አገራችን ውዲቷ ኢትዮጵያ ከአያት ቅድም አያቶች አጥንት ፍላጭ ተማግራ፣ አፈሯ በደማቸው ተለዉሶ ተቦክቶና ተጋግሮ ለሺዎች ዘመን የቆመች ሀገር ናት፡፡ ኢትዮጵያ የበርካታ ነገዶች ባህል ከባህል፣ሃይማኖት ከሃይማኖት ነገድ ከነገድ ተስበጣጥሮ ያቆማት የውህድ ማንነት ተምሳሌት ሀገር ናት፡፡ ይህም በልጆቿ ተጋድሎ ለዘመናት ከውጭ ወራሪ ሀይል ተጠብቃ በመቆየት የጥቁር ህዝብ ፈርጥ እንድትሆን አድርጓታል፡፡ ሆኖም በልጆቿ […]
ውስጠ ወይራው ያለመለወጥ ‹ለውጥ› (፪)
በክፍል አንድ መጣጥፌ ‹ለውጥ› እየተባለ የሚወራው ሀሰት መሆኑን አብራርቻለሁ፡፡ ‹ለውጥ› ተብየው ውስጠ ወይራ እንደሆነ እና ‹የለውጡ› መሪ ነኝ ባዩ አብይ አሕመድ ነብረው የወጡት ወያኔ የጣለውን እንቁላል እንደሆነ አብራርቻለሁ፡፡ በ‹ለውጥ› ሽፋን ‹ለውጥን› የመከላከል ቁልቁለቱ አያሌ ርዕዮተ ዓለማዊ፣ ሕገ መንግሥታዊ፣ ተቋማዊ እና ሥርዓታዊ መገለጫዎች አሉ፡፡ ከእነዚህም መካከል ሦስት መገለጫዎችን ቀንጭቤ እገልፃለሁ፡፡ አንደኛው የአዳፍኔነትና የአስቀጣይነት መንታ ስለት ሲሆን […]
የኢትዮ ቴሌኮም ሽያጭ ጥቅምና ጉዳት ጉዳይ ሙያዊ ቅኝት (ነብዩ ውብሸት)
አፄ ምኒሊክና የመጀመሪያው የስልክ ግንኙነት ኢትዮጵያ፣በ1886ዓ.ም፣በታላቁ ንጉሠ ነገሥት አፄ ምኒሊክ ዘመነ መንግሥት፣ የመጀመሪያውን የ477 ኪ.ሜ የስልክ መሥመር ዘርግታ፣“ጤና ይስጥልኝ ዐዲስ!! ጤና ይስጥልኝ ሐረር!!” ካስባለች፣126 ዓመታት ተቆጠሩ። አፄ ምኒሊክ፣ሀገሪቷን ያስተዳድሩ በነበሩበት ዘመን ያስገቧቸውን፣ዘመናዊ አሠራሮችንና ቴክኖሎጂዎችን ብዛት ስናይ፣አፄ ምኒሊክ፣“የሥልጣኔ ማግኔት ነበሩ!!” ለማለት እንችላለን። አፄ ኃይለሥላሴና የቴሌኮሙኒኬሽን እድገት ኹኔታ የቴሌፎን ቴክኖሎጂ ወደ ኢትጵያ የገባው፣በ1886 ዓ.ም በምኒልክ […]
“ገበታ ለሀገር” – ከዶሮና ዓሳ ወግ አንጻር(ከማለፊያ ደርሰህ)
ዶሮና ዓሳ የቀረበ ገበታ አይተው ወግ ይጀምራሉ:: በገበታው ላይ የቀረበው ምግብ የዕንቁላል ጥብስና ዓሳ ነው:: ዶሮው “ይህ ገበታ ጣፋጭ ሆኖ ትላልቅ መሳፍንትና መኳንንት ተደስተው እንዲመገቡ ለማድረግ የእኔ አስተዋጽኦ ከፍ ያለ ነው:: ምክንያቱም እንቁላሉን የጣለችው ሚስቴ ዶሮ ነች፤ እንቁላሉ የሁለታችንም ዶሮዎች አበርክቶ ነው” ብሎ ተኩራራ::ዓሳውም ተደንቆ “እናቱ የሞተችበትና ገበያ የሄደችበት እኩል ያለቅሳሉ” ብሎ ተረተና “ሰማህ ዶሮ፣ […]
ውስጠ ወይራው ያለመለወጥ ‘ለውጥ’ (በቃሉ ሰውመሆን (የሕግ ባለሙያ)
አቢቹ ሰብሮ የወጣው ወያኔ የጣለውን እቁላል ነው፤ በጥቅሉ ከ 1960 ዓ.ም ወዲህ እስካለንበት በተከሰተው እንዘጭ እቦጭ ውስጥ ኢትዮጵዊነትን ለከፍተኛ ኪሳራ የዳረገ እራስ በል እና እራስበሉን አስቀጣይ የሆነ ሽግግራዊ ክሽፈት አጋጥሞናል፤ አንደኛው የክሽፈት አንጓ የንጉሳዊ ስርአቱን አንጸባራቂ ውርሶች አዘምኖ ማሸጋገር ሲገባ ለአውዳሚ አቢዮት መዳረጋችን ሲሆን፤ ሁለተኛው ደግሞ የኢሕአዴግን አራሙቻ ስርአት የሚነቅል አብዮታዊ የስርአት ለውጥ ማዋለድ ሲገባን […]
