የባልደራስ ፓርቲው አቶ ካሳሁን ደስታ በፖሊስ ታገቱ

Balderas Latest News
የባልደራስ ፓርቲ የስራ አስፈፃሚ አባላት የሆኑት ዶ/ር በቃሉ አጥናፉና አቶ ስንታየሁ ቸኮል በወቅታዊ የፓርቲያችን እንዲሁም የሀገራችን ሁኔታ ላይ ተወያይተወዋል። ውይይቱን ከታች ባለው ሊንክ (Link) በመግባት ይከታተሉ።
የባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ በአሜሪካን የባልደራስ ደጋፊ የነበሩትን ጋዜጠኛ ዳዊት ከበደ ወዬሳን ድንገተኛ ሞት ሲሰማ ከፍተኛ ሀዘን ተሰምቶታል። አቶ ዳዊት ከበደ በጋዜጠኝነት ሙያ ለረጅም ጊዜ ሀገራቸውን በቅንነት ያገለገሉ ከመሆኑም ባሻገር ሙያቸውን አክባሪ፣ ትሁትና ቅን ሰው ወዳድ እንደነበሩ የሚታወቅ ነው።
ጋዜጠኛ ዳዊት ከበደ የፓርቲያችን መሥራችና ፕሬዚዳንት ከነበሩት ከጀግናው እስክንድር ነጋ ጋር የነበራቸው ሙያዊ ግንኙነትና ወንድማዊ ቀረቤታ ለብዙዎቻችን የባልደራስ አባላትና ደጋፊዎች የሚሰማንን ሀዘን የበለጠ የመረረ ያደርገዋል።ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ የተሰማውን መሪር ሀዘን እየገለፀ ለመላው ቤተሰባቸው ወዳጅ ዘመዶቻቸውና ጓደኞቻቸው መጽናናትን ይመኛል።
የትግል አጋራችን የነበሩትን የወንድማችን ነፍስ በአፀደ ገነት ያኑርልን!