የባልደራስ እጩ አባላት በወቅታዊ የምርጫ ጉዳዮች ዙሪያ ምክክር አደረጉ

የባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ በአዲስ አበባ ለፌዴራል የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና ለአዲስ አበባ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተወከሉ እጩዎች በዛሬው እለት በራስ አምባ ሆቴል ፤ መጪውን ምርጫ አስመልክቶ የተለያዩ መርኃግብር እየተካሄደ ይገኛል ።

የዕለቱ መርኃግብር በግፉ ለተገደለው የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ(አብን) ፓርቲ አባል ዕጩ ለአቶ በሪሁን አስፈራው የሕሊና ጸሎት በማድረግ የተጀመረ ሲሆን ፤ በአቶ በሪሁን አስፈራው የተደረገውን የግድያ ወንጀል የመርኅግብር ታዳሚዎች በጽኑ አውግዘዋል።
በራስ አምባ ሆቴል እየተካሄደ ያለው ዝግጅት ቀን ሙሉ የሚቀጥል ሲሆን ፤ የተለያዩ ዝግጅቶች ይካሄዳል ። በዝግጅቱ ላይ የባልደራስ እና የአብን ፓርቲዎች ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል ። የዚህን ዝግጅት ሙሉ ዘገባ የምናቀርብ ይሆናል ።
ድል ለእውነተኛ ዲሞክራሲ !!