ስለባልደራስ የእናቶች አስተያየት

እኔ-እናቴ ሰላም ዋሉ
ማዘር-እግዚያብሄር ይመስገን
እኔ- ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፖርቲ ዎች ነን ከተማችንን ለማዳን የእርስዎ ድምጽ ያስፈልገናል ካርድ አውጥተዋል ?!
ማዘር- አዎ አውጥቻለሁ ልጄ ባልደራስ ማለት የዛ ጀግና የእስክንድር ነጋ ነው አይደል ?!
እኔ-አዎ እናቴ !
ማዘር-እንደው ምን አድርግ ነው የሚሉት?
እኔ- እናቴ እውነትን ስለያዘ ይፈሩታል ፤ ከምርጫ ውጭ ለማድረግ ነው ። ሀሳብን ግን ማሰር አይችሉም የሱን ዓላማ ይዘን እስከመጨረሻው እንሄዳለን።
ማዘር- እየውልህ ልጄ አሰሩትም ፈቱትም እንመርጠዋለን። አሰሩትም ፈሩትም ያሸንፋቸዋል ። እሱ የፍቅር ሰው ስለሆነ ፍቅር ደሞ የአሸናፊነት መንገድ ነው ። አደራ እናንተም የአለቃችሁን መንገድ ተከተሉ ።በርቱ እናንተ እያላችሁ ሃገር አትፈርስም ተስፋ አለን ተባረኩ።
በአዳም ውጅራ